Tuesday, April 16, 2013

የተንቀሳቃሽ ስልክ 40ኛ ዓመት

እ ጎ አ በ 1875፣ የድምጽ ሞገድ በሽቦ ወደ ኤሌክትሪክ ሞገድ ተለውጦ እንዲተላለፍና ፤ ምልክቱ፤ በድምፅ ፤ በቃላት እንዲሰማ ያበቃውን ፤ ስልክ የተባለውን መሣሪያ ፣አለክሳንደር ግርሃም ቤል ከሠራ ወዲህ፤እ ጎ አ በ 1876 በተሽከርካሪ « ዲስክ»
እ ጎ አ በ 1875፣ የድምጽ ሞገድ በሽቦ ወደ ኤሌክትሪክ ሞገድ ተለውጦ እንዲተላለፍና ፤ ምልክቱ፤ በድምፅ ፤ በቃላት እንዲሰማ ያበቃውን ፤ ስልክ የተባለውን መሣሪያ ፣አለክሳንደር ግርሃም ቤል ከሠራ ወዲህ፤እ ጎ አ በ 1876 በተሽከርካሪ « ዲስክ» ላይ በኤሌክትሪክ ርዳታ፣ ምስል ማሳየት እንደሚቻል ጀርመናዊው Paul Gottlieb Nipkow ካሳወቀና እስኮትላንዳዊው ጆን ሎጊ ቤርድ፣ ራሱ በተናጠል ባካሄደው ተመሳሳይ ምርምር የቴሌቭዥንን ምሥጢር ለህዝብ ካሳዬ በኋላ፣በሩሲያዊ አሜሪካዊው ቭላዲሚር ዝቮሪኪን ፣ እ ጎ በ 1933 ኛዎቹ ዓመታት ፤ በ 1940ኛዎቹ ዓመታት ይበልጥ እስኪሻሻል ድረስ፤ የቴሌቭዥን ፕሮግራሞች እንዲሠራጩ ለማድረግ ማብቃቱ ተረጋገጠ። በኋላም እንደገና BAIRD ባለቀለም ምስሎችን በቴሌቭዥን ማሠራጨት የሚቻልበትን አብነት አግኝቶ ማሠራጨት እንደሚቻል
ሞቶሮላ RAZR
ካመላከበት ዘመን አንስቶ ተንቀሳቃሽ ምስል፣ በመስታውት ሣጥን የሚታይበት አስደናቂ የሥነ ቴክኒክ ግኝት በዓለም ውስጥ መዛመቱ አልቀረም። ከዚያም የኮምፒዩተር ዘመን ከተተካ በኋላ፤ ውሎ አድሮ ፤ መዳፍ በሚያክል የሥነ ቴክኒክ ውጤት ያለሽቦ ድምጽንም ምስልንም የሚያቀብሉም የሚያሠራጩም መሣሪያዎች ቀርበዋል።

የመታሰቢያ ድርጅቶች (ፋውንዴሽን) ከአፄ ምኒልክ እስከ መለስ

 የመታሰቢያ እና በጐ አድራጐት ድርጅቶች የ85 ዓመታት ጉዞ
ከመላው ዓለም በፊዚክስና ኬሚስትሪ፣ በሕክምናና በሥነ ፅሁፍ እንዲሁም በሰላም ዙርያ የላቀ አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰዎች ተመርጠው የሚሸለሙበት የኖቤል በጐ አድራጐት ድርጅት በተመሰረተ በ10ኛ ዓመቱ በኢትዮጵያም ተቀራራቢ ዓላማ ያለው “መታሰቢያ ድርጅት” ተቋቁሟል፡፡ አፄ ምኒልክ ከሞቱ ከአራት ዓመት በኋላ ልጃቸው ንግሥት ዘውዲቱ በ1910 ዓ.ም ለአባታቸው መታሰቢያነት አራት ኪሎ የሚገኘውን የበአታ ለማርያም ገዳም ቤተክርስቲያንን ማሰራት ጀመሩ፡፡
በግዛው ኃይለማርያም ተዘጋጅቶ የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ድርጅት በ1956 ዓ.ም ባሳተመው “ዳግማዊ ምኒልክ” የተሰኘ መፅሃፍ፤ የበጐ አድራጐት ሥራዎች በሦስት ዘርፎች ተከፍለው እንደሚከናወኑ ያመለክታል፡፡ የመጀመሪያው መታሰቢያቱን ማዕከል ያደረገው ነው፡፡ ግንባታው በተጀመረ በአስረኛ ዓመቱ በ1920 ዓ.ም የተጠናቀቀው የበአታ ለማርያም ገዳም ቤተክርስቲያን፤ የአፄ ምኒልክ፣ የእቴጌ ጣይቱ፣ የንግሥት ዘውዲቱ፣ የብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ የልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ አስከሬንና የተለያዩ ታሪካዊ ቅርሶች መቀመጫ ሆኗል፡፡ መታሰቢያ ድርጅቱ፤ በሁለተኛ ደረጃ ተግባራዊ ያደረገው መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ማቋቋም ሲሆን በ1925 ዓ.ም የተመሰረተው የአብነት ትምህርት ቤት፤ አገልግሎቱን ሳያቋርጥ እስካሁን በመቀጠል 80 ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡

የማይቃወሙ ተቃዋሚዎች በባትሪ ይፈለጋሉ!

*ኢህአዴግ - “ቀፎ ከእኔ፤ ማር ከእናንተ!” እያለ ነው
*መንገድ ትራንስፖርት - “መንገድ ከእኔ፤ ትራንስፖርት ከናንተ!” ይላል
ሁልጊዜ ምን እንደሚገርመኝ ታውቃላችሁ? የኢህአዴግ ነገር! አልሳካ ብሎት እንጂ ሁላችንንም እንደቀለበት መንገድ ጥፍጥፍ አድርጐ በአንድ ቅርፅ ቢሰራን ደስታውን አይችለውም፡፡ (ከፍቅሩ የተነሳ እኮ ነው!) በተለይ ተቃዋሚ ፓርቲዎችንማ---ሁሉንም በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ርዕዮተ ዓለም ቢያጠምቃቸው እፎይ ብሎ እንቅልፉን በለጠጠ ነበር፡፡ ግን እኮ አምባገነንነት አምሮት አይደለም (ኧረ ሲያልፍም አይነካው!) በነገራችሁ ላይ … በአምባገነኖች ላይ ባደረግሁት Formal ያልሆነ “ባህላዊ ጥናት”፤ አብዛኞቹ አምባገነኖች የእግዚአብሔርን ስም ደጋግመው መጥራት እንደሚወዱ አረጋግጬአለሁ፡፡ (ማጭበርበርያ እኮ ነው!) ለምሳሌ ባለፈው ሳምንት በካንሰር ህመም የሞቱት የቬንዝዌላው የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሁጎ ቻቬዝና የቀድሞው የኡጋንዳ ፕሬዚደንት ኢዲ አሚን ተጠቃሽ ናቸው - የፈጣሪን ስም በመጥራት፡፡ አሚንማ ከእግዚአብሔር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አደርጋለሁ ባይ ነበሩ፡፡

ለኢቴቪ ዓመቱን ሙሉ “April the fool” ነው!

ሰሞኑን የተከሰተ ዜና ነው - እዚህ ሳይሆን ፈረንጆቹ አገር፡፡ ሁለት ታዳጊ ፍቅረኛሞች ናቸው አሉ፡፡ የፍቅር ጓደኝነት ከመሰረቱ ብዙ አልቆዩም፡፡ ግን ሲዋደዱ ለጉድ ነው፡፡ (እንደ ኢህአዴግና ተቃዋሚዎች እንዳትሉኝ!) ባለፈው ሰኞ ግን በጨዋታ መሃል በተፈጠረ አለመግባባት እሷ እሱን አንገቱ ላይ በስለት ወግታው ወህኒ ወረደች አሉ (የአፍሪካ ፖለቲካ አይመስልም?) አያችሁ እንዲህ በጨዋታ መሃል ያልተጠበቀ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡ አንዳንዴ ዓይን ሊጠፋ ወይም እግር ሊሰበር ይችላል፡፡ ባስ ሲል ህይወትም ይጠፋል፡፡ በፍቅር ጨዋታ እንዲህ ካጋጠመ በፖለቲካ ጨዋታ ምን ሊያጋጥም እንደሚችል አስቡት፡፡
እቺን እቺንማ ከእኛ በላይ ማን ያውቃታል? ምንም ቢሆን እኮ የአፍሪካ ልጆች ነን! (የአራዳ ልጅ እንዲሉ) የጨዋታው አባቶች የአፍሪካ አምባገነን መሪዎች ከሆኑ ደግሞ ነገርዬው የከፋ ይሆናል - የመረረ!! ለምን መሰላችሁ? መቼ እንደሚያመሩ፤ መቼ ከፍቅር ወደ ጥላቻ እንደሚሸጋገሩ ፈጽሞ አታውቁም፡፡ ኳስ ይዞ የነበረው እጃቸው በምን ቅጽበት ጠብመንጃውን አፈፍ እንዳደረገ ፈጣሪያቸው ብቻ ነው (የራሳቸው ፈጣሪ ይኖራቸዋል ብዬ እኮ ነው!) የሚያውቀው (“አድነነ ከመዓቱ” ማለት ይሄኔ ነው!) ይኸውላችሁ የእኔ ነገር የፍቅረኞቹን ሳልጨርስላችሁ ፖለቲካ ውስጥ መሰስ ብዬ ገባሁላችሁ፡፡ (ፖለቲካ አሳሳች እኮ ነው!) እናላችሁ.. ሁለቱ ፍቅረኛሞች ሲገናኙ ሁሉም ነገር አማን ነበር፡፡ በተለይ እሱ ፍቅር እንጂ ሌላ አልጠበቀም፡፡

የካፒታሊዝም የኑሮ ፍልስፍና!

በዓለማችን ውስጥ የሚገኘው አጠቃላይ የምግብ ክምችት በዓለም ላይ ያሉ ሰዎችን በሙሉ ማጥገብ ይችል ነበር፤ ነገር ግን አብዛኛው የዓለማችን ሃብት በጥቂት ግለሰቦች ቁጥጥር ስር በመውደቁ ጥቂቶቹ የቅንጦት ኑሮ ሲኖሩ አብዛኛው ደሃ ህዝብ ግን በረሃብ አለንጋ ይገረፋል፤ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ባለመኖሩ፤ በማለት ማርክሲስቶች እኩልነት ደሃና ሃብታምን እኩል በማድረግ ማረጋገጥ እንደሚቻል ያስተምራሉ፡፡ በሌላ በኩል የካፒታሊዝም መስራቾች የግል ሃብት የማፍራት መብትን በማረጋገጥ የሃብታሞችና የድሆች መደቦችን በመፍጠር፣ ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍልን ማስፈን እንደሚቻል ወይም እኩልነትን በሃብት መበላለጥ ማምጣት እንደሚቻል ይሞግታሉ፡፡ የካፒታሊዝም ሆነ የሶሻሊዝም መስራቾች ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልንና እኩልነትን ይሰብካሉ፡፡

ያልተጠናው የኢትዮጵያውያን ፍልስፍና

ሀገራችን ኢትዮጵያ ገና ያልተጠኑ የበርካታ ጥንታዊ ሥነጽሁፎች ባለቤት ናት፤ ማጥናት አቅቶን ሌሎች አጥንተው የቅጂ መብቱን ከመውሰዳቸውና የታሪክ ክፍትት ተፈጥሮ በመጪው ትውልድ ተወቃሾች ከመሆናችን በፊት የዘርፉ ምሁራን ጥናትና ምርምር በማካሄድ፣ ዩኒቨርስቲዎች ጉዳዩን የምርምር አቅጣጫቸው ውስጥ በማስገባት፣ ዜጎችም ጥንታዊ የጽሁፍ ሃብታችንን አስፈላጊነት ተገንዝበን ከዘራፊዎች በመጠበቅ ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል፡፡ ኢትዮጵያ ዘመናትን ያስቆጠሩ ሥነቃላዊና የጽሁፍ ፍልስፍናዎች ባለቤት ናት፡፡ ከአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች በተለየ መልኩ በርከት ያሉ የፍልስፍና ስራዎችን በመስራት በቀዳሚነት የምትጠቀሰው ኢትዮጵያ፤ በጥንታዊው የግእዝ ቋንቋ ከተጻፉት የፍልስፍና ስራዎቿ መካከል ከፊሎቹን በትውልድ ካናዳዊ፣ በምርጫ ደግሞ ኢትዮጵያዊ የሆነው ፕሮፌሰር ክላውድ ሰምነር ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ በመተርጎም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቁ ሲያደርግ፤ ሌሎች በርካታ በግዕዝና በአረብኛ ቋንቋዎች የተጻፉ የጽሁፍ ስራዎች በጥንታዊ ቤተእምነቶችና ቤተመዛግብት ውስጥ ተቀምጠው ክላውድ ሰምነርን የመሰሉ ፈላስፎችንና የጥንታዊ ጽሁፎች ተመራማሪዎችን (philologists) እይታ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

“ወሬ ይሮጣል!” - የበአሉ ነገር!


  • ፊያሜታ
አነበብኩት፡፡ ደግሜ አነበብኩት፡፡ መላልሼ አነበብኩት፡፡ ለምን እንደሆነ አላውቅም ያነበብኩትን ነገር ለማመን አቃተኝ፡፡ ሉጫ ፀጉራቸው እርስ በርሱ ተገማምዶ ጀርባቸው ላይ የወደቀ፣ ወዝ የጠገበ ላመነት ያገለደሙ፣ እህል የራቀው አንጀታቸውን በሰንሰለት ሸብ ያደረጉ፣ ፂማቸውን ያንዠረገጉ፣ ከአለም ተነጥለው በራቸውን የዘጉ…እንዲህ ያሉ መናኝ ---- በአሉ ግርማን ማሰብ አቃተኝ፡፡ “አበቃ” ብሎ በዘጋው ጦሰኛ ስራው ሰበብ፣ የእሱም ነገር እንዳበቃ ከተነገረለት፤ ከዚያኛው በአሉ የቀጠለ ሌላ በአሉ አልመጣልህ አለኝ፡፡ ከተቋጨ ደራሲነትና ጋዜጠኝነት የቀጠለውን የበአሉ መናኝነት ማሰብ ተሳነኝ፡፡ ባለፈው ሰኞ ምሽት አንድ ወዳጄ በፌስቡክ የላከልኝ “ጉድ” “በአሉ ግርማ በጣና ደሴት ገዳማት የመናኝ ህይወት እየገፋ ተገኘ” የሚል ነበር፡፡ ይህን “ጉድ” ለማመን ቸግሮኝ ጥቂት እንደተወዛገብኩ፣ ነገርዬው “የሚያዝያ ልግጥ” (April the fool) ሊሆን እንደሚችል ገመትኩ፡፡

Wednesday, April 3, 2013

ከሚድሮክ ኢትዮጵያ ከ632 ሚሊዮን ብር በላይ የግብር ዕዳ ይፈለጋል

ሚድሮክ ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ከንግድ ትርፍ ግብርና ከተጨማሪ እሴት ታክስ ከ632 ሚሊዮን ብር በላይ ዕዳ በመንግሥት እንደሚፈለግበት የኩባንያው ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡
ሚድሮክ ይህንን ክፍያ እንዲፈጽም የተነገረው ለባለኮከብ ሆቴሎቹ መሆኑ ታውቋል፡፡

የኩባንያው ምንጮች እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በቅርቡ ለሚድሮክ ኢትዮጵያ በላካቸው ሦስት የትርፍ ግብር ውሳኔ ማስታወቂያዎች የተጠቀሰው ገንዘብ እንዲከፈል ጠይቋል፡፡

የድምፅ ብክለት

የድምፅ ብክለት የአየር ብክለትን ተከትሎ ያለ በዓለም ሁለተኛው ግዙፍ የአካባቢያችን ብክለት

ይህንን የብክለት ዓይነት የሚፈጥረው ድምፅ ያልተፈለገና በሰው መረበሽን የሚፈጥር ማንኛውም ዓይነት ድምፅ ነው፡፡

እንዲህ ዓይነት ድምፆች መደበኛውን የሕይወታችንን እንቅስቃሴ ይጎዳሉ፤ ያስተጓጉላሉ፣ እንቅልፍ ይነሱናል፤ ውይይቶቻችንንና መደማመጣችንን ይቀንሣሉ፤ በአጠቃላይ የአኗኗራችን ሁኔታ የተረበሸ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡

ዓይነት ነው፡፡

የኣበሾች ሁሉ የኩራት ምንጭ






የኣበሾች ሁሉ የኩራት ምንጭ
የኣክሱም ስርወ መንግስት በኣፍሪቃ ሰሜናዊ ምስራቅ የሚገኝ እጀግ ጠቃሚ የንግድ ብሔር ነበር፡ ፡ ስርወ መንግስቱ በ300 ዓ.ዓ. ኣከባቢ ኣብቦ በ 300 ዓ.ም. ኣከባቢ ከፍተኛ የስልጣኔ ድረጃ የደረሰ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡ ከሮማ ስርወ መንግስትና ከጥንታዊዋ ሕንድ ጋር የንግድ ግንኝነት የነበረው ስርወ መንግስት የራሱ የመገበያያ ገንዘብ ነበረው፡ ፡ የኣክሱም ስርወ መንግስት በደቡባዊ የኩሽ ግዛት ላይ የበላይነትን ይዞ የቆየ ከመሆኑም በላይ የኣረቡን የባሕር ሰላጤ በከፊል በፖሊቲካ መቆጣጠር የቻለ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡
የኣክሱም ስርወ መንግስት በኣፍሪቃ ሰሜናዊ ምስራቅ የሚገኝ እጀግ ጠቃሚ የንግድ ብሔር ነበር፡ ፡ ስርወ መንግስቱ በ300 ዓ.ዓ. ኣከባቢ ኣብቦ በ 300 ዓ.ም. ኣከባቢ ከፍተኛ የስልጣኔ ድረጃ የደረሰ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡ ከሮማ ስርወ መንግስትና ከጥንታዊዋ ሕንድ ጋር የንግድ ግንኝነት የነበረው ስርወ መንግስት የራሱ የመገበያያ ገንዘብ ነበረው፡ ፡ የኣክሱም ስርወ መንግስት በደቡባዊ የኩሽ ግዛት ላይ የበላይነትን ይዞ የቆየ ከመሆኑም በላይ የኣረቡን የባሕር ሰላጤ በከፊል በፖሊቲካ መቆጣጠር የቻለ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡

መድረክ ማኒፌስቶ ኣወጣ



መድረክ ‹‹የኢትዮጵያ ወቅታዊና መሠረታዊ ችግሮች የመፍቻ አቅጣጫዎች ማኒፌስቶ›› የሚል ስያሜ የሰጠውን ሰነድ ማክሰኞ ዕለት ይፋ አደረገ፡፡ኦነግ ኣንጋፋ ኣባላት " ለ እዉነተኛ ፈዴራሊዝም" የሚታገል ኣዲስ ድርጅት ማቋቋማቸውን ይፋ ኣድረገዋል፡ ፡

 ማኒፌስቶው አገሪቱ በመስቀለኛ መንገድ ላይ ትገኛለች፡፡ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ፊት የበለጠ ኣደጋ ተደቅኗል ይላል፡፡
ማኒፌስቶውን ለማስተዋወቅ ከቀረቡት የፓርቲው አመራሮች መካከል ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ ‹‹የመለስ ራዕይ ለኢትዮጵያ የውድቀት መንገድ ነው›› በማለት በአሁኑ ወቅት የገዥው ፓርቲ አመራሮች እየተከተሉ የሚገኙትን በመለስ አስተምህሮ የአገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት የማስቀጠል መርህን ወቅሰዋል፡፡

Tuesday, April 2, 2013

ሽብርተኞች ይፈለጋሉ!!

የኣሜሪካ ፌደራል የምርመራ ቢሮ ሁለት የኣሜረካ ዜጎች የኣሸባሪው ኣልሸባብ ኣባላት ጠቁሞ ላስያዘ 10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት እንደሚሰጥ ኣስታወቀ፡ ፡ ኣልሸባብ የጎረቤት ኣገራችንን ማዕከላዊና ደቡባዊ ክፍል ተቆጣጥሮ ከ 2008 ጀምሮ ተከታታይ ጥቃቶችን የፈጸመ ኣሸባሪ ድርጅት ነው፡ ፡ኣልሸባብ በኣሜሪካም በኢትዮጵያም እንደ ኣሸባሪ ድርጅት በይፋ የተፈረጀ ብቸኛ ሶማሊያዊ ድርጅት ነው፡ ፡
ሁለቱ ኣሜካውያን ተፈላጊ ኣሸባሪዎች ጀሃድ ሙስጦፋና ዑመር ሓማሚ ናቸው፡ ፡

የምርመራ ቢሮው ሁለቱም ኣሁንም ሶማሊያ እንደሚገኙ ያምናል፡ ፡ 
ባለ ሰማያዊ ዓይን ቀለም ተፈላጊዎቹ በዜግነት ኣሜሪካውያ ሲሆኑ 1 በካሊፎርንያ የሳንዲየጎ ኗሪ ነበር፡ ፡

Monday, April 1, 2013

ተማሪዎች ብሪትሽ ካውንስልና መንግሥትን ለመክሰስ ዝግጅት እያደረጉ ነው

ከእንግሊዙ ካምብሪጅ ኮሌጅ ዲግሪ ለማግኘት በማሰብ በአገር ውስጥ በትብብር ሥልጠናውን ይሰጥ ከነበረ ተቋም የተልኮ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩና የተመረቁ መንግሥትን ጨምሮ፣ ተቋሙንና የብሪትሽን ካውንስልን ፍርድ ቤት ለማቆም እየተዘጋጁ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡
ዘመን ዲቨሎፕመንት ኤንድ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የተሰኘው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በድንበር ዘለል ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ዕውቅና ተሰጥቶት፣ 400 ያህል ተማሪዎችን ሲያስተምር ቆይቷል፡፡ ሆኖም ካለፈው ታኅሳስ ወር 2005 ጀምሮ ዕውቅናው መሰረዙን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡ ለዚህ ውሳኔው ኤጀንሲው ምክንያት ያደረገው ከካምብሪጅ ኢንተርናሽናል ተሰጥቶኛል ያለውን የታደሰ የዕውቅና ማረጋገጫ፣ ዘመን ኢንስቲትዩት እንዲያቀርብለት ቢጠይቅም ሊቀርብለት ባለመቻሉ እንደሆነ አስታውቆ ነበር፡፡

መሐንዲስ አልባው መተካካት

የመንግሥትም ሆነ የግሉ ሚዲያ የኢሕአዴግ ጉባዔ ዜናዎችን በማሰራጨት ተጠምደዋል፡፡ በተለይ አራቱ የግንባሩ አባል ድርጅቶች በበላይነት የሚመሩባቸው ክልሎች ዋና ከተሞች ላይ የየራሳቸው ጉባዔያቸውን እያካሄዱ ነበር፡፡
በአንዳንድ አባል ድርጅቶች ጠንካራ አመራሮችን ለማስወገድ፣ በሌሎች ደግሞ የቀድሞውን አመራር ለማጠናከር ጥቅም ላይ ውሏል በሚል እያነጋገረ ነው፡፡

ድርጅቱ ከ20 ዓመታት በፊት በ1981 ዓ.ም. በሕወሓት ፊታውራሪነት ከተመሠረተ ጊዜ ጀምሮ በበላይነት የመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የፓርቲው ቀጥሎም የመንግሥት ከፍተኛ ሥልጣናቸው ጥያቄ ውስጥ ገብቶ አያውቅም፡፡ የሕወሓትንና የኢሕአዴግን የፓርቲ የውስጥ የፖለቲካ አጀንዳ ብቻም ሳይሆን የአገሪቱን የፖለቲካ ዕጣ ፈንታ የሚወስን አቅጣጫ የሚያስይዙ፣ የፖለቲካውም፣ የኢኮኖሚውም፣ የውጭ ግንኙነቱም መሐንዲስ ሆነው ቆይተዋል፡፡

 የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ‹‹ዲሞክራሲያዊነታቸው›› በብዙዎች ዘንድ አከራካሪ ቢሆንም፣ ሥልጣንን የመጠቅለል ችሎታቸው፣ ተፎካካሪያቸውን በዕውቀትና በንግግር ብልጠት ክህሎታቸው ልቀት ግን ለጭፍን ደጋፊዎቻቸውም ለአክራሪ ጠላቶቻቸውም የሚያጠያይቅ አልነበረም፡፡ ይህ ከፍተኛ የአመራር ብቃታቸው፣ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕውቀታቸውና ተናግሮ የማሳመን ክህሎታቸው ከፓርቲም ከአገርም አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ አስመስክረው አልፈዋል፡፡ ምናልባትም በመጨረሻ የሥልጣን የሕይወት ዘመናቸው በዓለም ተፅዕኖ ፈጣሪው ሰው ሆነው ነበር፡፡

‹‹የአገሬ ፕሬዚዳንት መሆን እችላለሁ ብዬ መናገሬ በራሱ ትልቅ ነገር ነው›› ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ፣ የፓርላማ ብቸኛው የግል ተመራጭ

‹‹የአገሬ ፕሬዚዳንት መሆን እችላለሁ ብዬ መናገሬ በራሱ ትልቅ ነገር ነው›› ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ፣ የፓርላማ ብቸኛው የግል ተመራጭ

የቀድሞው የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ በምርጫ 2002 ዓ.ም. ተወዳድረው በማሸነፍ በፓርላማ ብቸኛ የግል ተመራጭ ናቸው፡፡
በፓርላማው ውስጥም የሳይንስ፣ የመገናኛና ቴክኖሎጂ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮ ጀርመን ወዳጅነት ኮሚቴን በምክትል ሊቀመንበርነት ይመራሉ፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን በመወከል የፓን አፍሪካ ፓርላማ አባል ሲሆኑ፣ በወቅታዊ አገራዊና አኅጉራዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች የማነ ናግሽ ዶ/ር አሸብርን አነጋግሯቸዋል፡፡

ሪፖርተር፡- በ2002 ዓ.ም. በተደረገው ብሔራዊ ምርጫ ተቀናቃኝዎን አሸንፈው የፓርላማ አባል ከሆኑ ከሁለት ዓመት በላይ ሆኖታል፡፡ ፓርላማው በአግባቡ እየሠራ አይደለም ይባላል፡፡ በተለይ ደግሞ የሳይንስ፣ የመገናኛና ቴክኖሎጂ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢነትዎን እንዴት ይገመግሙታል?

ዶ/ር አሸብር፡- እንደ ምክር ቤቱ አባል ፓርላማው በአግባቡ እየሠራ ነው የሚል እምነት ነው ያለኝ፡፡ በእኛ ቋሚ ኮሚቴም ተጠሪነታቸው ለእኛ የሆኑት ሚኒስትር መሥርያ ቤቶች ለእኛ ሪፖርት ያቀርባሉ፡፡ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ሚኒስቴር፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ እንደ የኢትዮጵያ ጨረር መከላከያ፣ ደረጃ መዳቢዎች፣ አዕምሮአዊ ንብረት የመሳሰሉት ተጠሪነታቸው ለእኛ ነው፡፡ የእነሱን ሪፖርት እናዳምጣለን፡፡ ዕቅዳቸውንም እናያለን፡፡ መሻሻል ያለበትን እንጠቁማለን፡፡ የሩብ ዓመት፣ የስድስት ወራት እንዲሁም የአንድ ዓመት ክንውናቸውንም እንገመግማለን፡፡ ግብረ መልስም እንሰጣቸዋለን፡፡ ጠርተን እናነጋግራቸዋለን፡፡ አንዳንዴም ‹‹ሰርፕራይዚንግ ቪዚት›› (ድንገተኛ ጉብኝት) እናደርጋለን፡፡ መደበኛ ሥራም እንሠራለን፡፡ ሌላም በምክር ቤት ደረጃም መደበኛም አስቸኳይ ስብሰባዎችም አሉን፡፡ ይኼ እንግዲህ ዕቅድ ተይዞለት ነው የሚሠራው፡፡ ስለዚህ ምክር ቤቱ ሥራውን እየሠራ ነው፡፡

‹‹መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ!›› በታሪክ አጻጻፍ ስልትና የተዛቡ የሁነቶች ትንታኔ ላይ የተሰጠ ሙያዊ ሒስ

በሳሙኤል ኪዳነ፣ አክሱም ዩኒቨርሲቲ
እውን ግን ታሪክ ይከሽፋል?
የዚህ ጽሑፍ ዋና መነሻ የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በኋላ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመባል የሚታወቀውን ተቋም በጂኦግራፊ የትምህርት ዓይነት በአስተማሪነት ሞያ ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ፣ በአሁኑ ወቅት በጡረታ የሚገኙት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ታኅሳስ 2005 ዓ.ም. ላይ
‹‹መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ›› በሚል ርእስ ለሕትመት ባበቁት መጽሐፍ ላይ በተነሱት ታሪካዊ ጉዳዮች ላይ ያለኝን የግል አስተያየት መሠረት በማድረግ መስተካከል ያለባቸውን ጉዳዮች ላይ መረጃን ብቻ መሠረት ያደረገ ሙያዊ ሒስ ለመስጠት ነው፡፡

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም ማን ናቸው? ለሚለው ጉዳይ ብዙ ማብራርያ ለመስጠት ባልደፍርም ሆኖም ግን እሳቸው በሙያቸው ያበረከትዋቸው ሥራዎች ግን ምንድን ናቸው? ለሚለው ጥያቄ ለዚህ ጽሑፍ አንባብያን ይረዳ ዘንድ በ2003 ዓ.ም. ራሳቸው ካሳተሙት ‹‹አገቱኒ ተምረን ወጣን›› በሚለው መጽሐፋቸው ተዘርዘረው የሚገኙትን ነጥቦች ማየቱ ጠቃሚ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡

ከትዝታ እስከ ሻላዬ

የታወቀው ስታር ባክስ ቡና ቤት ቁጭ ብሎ በጣዕሙ ጠንከር ያለውንና ሽታው የሚያውደውን ይርጋ ጨፌን ቡና መጠጣት በምዕራቡ ዓለም የተለመደ ነው፡፡
ጥያቄው ግን ከቡናው ጀርባ ያሉት ሰዎች እነማን ናቸው? ይኼንን ቡና የሚያመርቱት ገበሬዎቹስ ምን ዓይነት ሕይወት አላቸው? ሙዚቃቸውስ ምን ዓይነት ነው? የሚለውን ጥያቄ የሚጠይቀው ምን ያህል ሰው ነው፡፡

ውጭው ዓለም የሚኖሩ ሰዎችን ተወት እናድርጋቸውና ምን ያህል ኢትዮጵያውያን ናቸው ከዚህ ከሚጥም ቡና ጀርባ ያሉ ሰዎችን የአኗኗር ዘዬ የሚያውቁ በደቡብ ክልል ጌዴኦ ዞን ውስጥ የምትገኘው ይርጋ ጨፌ በቡና ታዋቂ ብትሆንም በሕዝቧ አኗኗር ወይም በሙዚቃ አትታወቅም፡፡ እንደ ሌሎች አካባቢዎች የተመዘገበ ታሪክ ወይም ሙዚቃ ስለሌለ ይሔንን ለማወቅ ቦታው ላይ መሔድ ያስፈልጋል፡፡

ሌላው ዓለም ባህላቸውን ወይም ዘፈናቸውን አወቀላቸው አላወቀላቸው ግድ ባለመስጠት ከአዲስ አበባ 400 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ለምና አረንጓዴ ቦታዋ ይርጋ ጨፌ ሕፃናት በአዲስ ዓመትና መስቀል ‹‹አና ዴስኮ›› የሚል ዘፈን እየዘፈኑ ያድጋሉ፡፡ ዘፈኑ በይርጋ ጨፌ ብቻ ሳይሆን በዲላ ከተማ እንዲሁም በጌድኦ ዞን ታዋቂ ነው፡፡ አብርሃም በላይነህ ቦታውን ከጐበኘ በኋላ ዘፈኑና ዜማው አዕምሮ ውስጥ ተቀርፆ ቀረ፡፡ እናም አንድ ነገር ለማድረግ ወሰነ፡፡ ይሔንን ዘፈን የራሱን ነገሮች ጨምሮ ታዋቂ የሆነውን ሻላዬ (ቆንጅዬ) የሚለውን ዘፈን አወጣ፡፡

ይሓ

በቅድመ አክሱም ታሪክ የይሓን ሥልጣኔ በ100 ዓመት ወደፊት የሚያስቀድም 2 ሺሕ 800 ዓመት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ ሕንፃ በቁፋሮ መገኘትን ያበሰሩት ኢትዮጵያውያንና ጀርመናውያን ባለሙያዎች ናቸው፡፡ ያገኙትም በይሓ አካባቢ ግራት በዓል ግብሪ በተሰኘ ስፍራ ነው፡፡ እንደተመራማሪዎቹ ግኝቱ በኢትዮጵያና በየመን መካከል ቀድሞ በነበረ ግንኙነት  የሚናገሩ መላምቶችን የሚቀይርና የኢትዮጵያን ታሪክ የሚያድስ ይሆናል፡፡

ከአክሱም ሰሜን ምሥራቅ አቅጣጫ 56 ኪሜ ርቆ የሚገኘው ይሓ ከጥንታዊው የአክሱም ሥርወ መንግሥት በፊት የነበረው የደአማት ሥርወ መንግሥት መቀመጫ እንደነበረ ይነገራል፡፡ በሌላ በኩል በይሓ አሁንም ድረስ ፍራሹ ቆሞ የሚታየው ምኩራብ አለ፡፡ ምኩራቡ ‹‹አልሙቃህ›› ለተባለ የጨረቃ አምላክ አምልኮት ይፈጸምበት እንደነበረ በጥናት ተረጋግጧል፡፡

የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ኤጀንሲ አንድ ሕትመት እንዳሳየው፣ ይሓ የጥንታዊው የደኣማት መንግሥት መቀመጫ ማዕከል ሆኖ ያገለገለ ሲሆን፣ መንግሥቱም ከክርስቶስ ልደት በፊት ከስምንተኛ እስከ ሦስተኛ ክፍለ ዘመን እንደቆየ ጥናቶች ያወሳሉ፡፡ ይሓ በወቅቱ የንግድ፣ የእርሻ፣ የሥነጥበብና የአስተዳደር ማዕከል ሆኖ በማገልገሉ በላቀ ደረጃ ላይ ደርሶ እንደነበር የሚያሳዩ አሻራዎች እስካሁን ይታያሉ፡፡

የወደቀችው ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ

ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነፃ ከወጣችበት እ.ኤ.አ ከ1960 ወዲህ መረጋጋትን አስተናግዳ አታውቅም፡፡
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም የተፈረካከሰች ግዛት ይላታል፡፡ በዓለም በዕድገታቸው ወደኋላ ከቀሩ አገሮችም ከመጨረሻው ሥፍራ ትመደባለች፡፡ ይህ የሆነው ደግሞ አገሪቷ ሀብት አጥታ አይደለም፡፡ ምንም እንኳን የባሕር በር ባይኖራትም በውኃና በማዕድን ሀብቷ አንቱ የተባለች ነች፡፡

ለግብርና ምቹ ሥፍራም ናት፡፡ ሆኖም በአገሪቷ ለረዥም ጊዜያት ተንሰራፍቶ የሚገኘው ሙስና የአገሪቷን የጣውላና የአልማዝ ኢንዱስትሪ አቀጭጮታል፡፡ ያልተነኩ የአገሪቷ የደን ሀብቶች በውስጣቸው የያዙዋቸው ዝሆንና ጐሬላ የአገሪቱ መገለጫዎች ቢሆኑም፣ አገሪቷ ከተፈጥሮም ሆነ ከሰው ሀብቷ ተጠቃሚ መሆን አልቻለችም፡፡ ይልቁንም ሕዝቧ በአገሪቱ በየጊዜው በሚያገረሸው ብጥብጥ ለሞትና ለስደት ተጋልጧል፡፡

ምሁራኑ ከተፈረካከሰች ግዛት የሚመድቧት ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በተደጋጋሚ መፈንቅለ መንግሥት አስተናግዳለች፡፡ በአንድ ወቅት ራሳቸውን ንጉሥ አድርገው የሾሙት ዦን ቤደል ቦካሳ በፈረንሳይ አጋዥነት በዴቪድ ዳኮ በተመራ መፈንቅለ መንግሥት እ.ኤ.አ በ1979 ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ አገሪቷ የተለያዩ መሪዎችን ብታፈራርቅም አልሆነላትም፡፡ ግጭትን ማርገብ አልቻለችም፡፡ ሕዝቧ ከሽምቅ ውጊያ አልወጣም፡፡

በምንበላው ሲገርመን በምንተነፍሰው?

እነሆ ዛሬ ደግሞ ከመገናኛ ወደ ገርጂ ልንሳፈር ነው። ፀሐይን ሰሞነኛው ደመና ሸፍኗታል። ልክ አንዳንዱን እውነታ ሰሞነኛ ማስተባበያ እንደሸፈነው።
ኑሮ፣ ኑሮ ሰውን ወዝውዞ ወዝውዞ የሆነ የሕይወት ቱቦ ውስጥ ጥሎ የረሳው ይመሳለል። መንገዱ ላይ ቆሜ በትርምሱና በጫጫታው መሀል የማሰላስለው ከአድማስ ወዲህ ማዶ ስላለው ስለእኛ ስለሰው ልጆች ትግል ነው። ሁሉም ነገር በትግል ሲባጎ ተጠፍንጎ የተሳሰረ ሆኖ ይታየኛል።

ሁሉን የሚችለው ብርቱው የሰው ልጅ በአልበገር ባይነት ፅናትና መንፈስ ለመኖር ግብግብ እንደገጠመ አየዋለሁ። ቁልቁል ወደቤቷ የምትሰደደው ጀንበር የምትነግረኝ ግን ሌላ ነው። የሽንፈት ደመና የመከራ ዝናብ ቋጥሮ እኛ ላይ የሚለቀው አስመስላ ታሳየናለች። ለታክሲ ሠልፍ የያዘው መንገደኛም ገልመጥ እያለ በጠቋቆረው  ደመና ውስጥ አንድ ነገር ፈልጎ ያጣ ይመስላል። ‹‹ይህ ነው የእኛ ሕይወት?›› ትላለች አንዲት ቀጭን ጠይም ረዢም ወጣት። ያለ ዕድሜዋ የተሸበሸበ ቆዳዋን ስመለከት ብዙ ያልተኖሩ ልጅነቶች ይታወሱኝ ጀመር። ‹‹አይ እናት አገሬ! ስንቱን ያለ ዕድሜው አገረጀፍሽው?›› ይላል ሳላየው ልጁቱን እንደ እኔው ሲያስተውላት የቆየ ጎልማሳ። ‹‹የቱ ነው የእኛ ሕይወት ማለት?›› ትላታለች ግራ የተጋባች ጓደኛዋ። ‹‹ያ ሩቅ ያለው ደማና ነዋ! ከደመናው ጀርባ ፀሐይ እንዳለች እርግጠኛ የሆንበት ደመና።

ብሶት ሲገነፍል

ዛሬ የምንጓዘው ከስታዲየም ወደ ጎተራ መስመር ነው። ምድርና ሰማይ እንደተጠፋፉ ዘመዳማቾች በዝናብ ወሬያቸውን እንደተያያዙት ነው።
ነዋሪው ከቦይ ተርፎ በሚፈስ ጎርፍ ውስጥ እየተንቦጫረቀ ታክሲ ይጠብቃል። ድንገት ተራ አስከባሪው መጥቶ፣ ‹‹ተሠለፉ በዝታችኋል!›› ብሎን ዘወር ከማለቱ፣ ‹‹ወይ ትዕዛዝ ብንሠለፍ ለራሳችን ምን ይቆጣናል?›› ብሎ አንዱ ተናገረ። ‹‹ይገርማል! መቼም ሐበሻ አዲስ ነገር መቀበል ሞቱ ነው። ቆይቶ ግን የትናንቱን አዲስ በታላቅ መስዋዕትነት ይጠብቀዋል። ሰው ትናንት ለምን እንሰለፋለን ብሎ እሪ እንዳላለ አሁን በውዴታ!?›› ብሎ ሌላው ግርምቱን ይተርካል። ‹‹ምን እናድርግ ታዲያ? ወደን መሰለህ? ‘ወዳ አይደለም እኮ ቅጠል ስትበጠስ የምትበሰብሰው’ ሆኖብን እንጂ!›› ስትል አንዲት ሴት ትመልስለታለች።

እስከ መቼ ከአንገት በላይ?

ሰላም! ሰላም! አንድ ወዳጄ ‹‹ይኼን ሳምንት ‘ቢቢሲ’ ይዘንባል ብሎ ተንብዮአል፤›› ብሎ እንዲሁ አንጋጦ ውኃ ያዘለ የደመና ክምር ሲጠብቅ ሰነበተ።
ይገርማል ‘ኢቲቪ’ ተናግሮት ቢሆን ኖሮ እንኳን ከሰማይ ከቧንቧ ውኃ ባልጠበቀ ነበር።

አፈር ልሁንለትና የዛሬ ስንት ዓመት ገደማ አንድ ጋዜጠኛ ጓደኛ ነበረኝ። ይህ ወዳጄ አብዝቶ ስለሙያው ክብርና ትልቅነት ያጫውተኝ ነበር። እና አሁን ሳስበው እንኳንም ቆሞ አላየ እላለሁ። ምኑን ካላችሁ መልሱ ‹‹ሁሉን!›› የሚል ነው። እንኳን እሱ ሌላውም ቢሆን። ጥቂቶች ሊባል በሚያስቸግር ሁኔታ ሆዳቸውን እንጂ የሙያ ክብራቸውና ግዴታቸውን የረሱና የስንቱን ሙያ ስም ክፉኛ ያጠፉ አሉም አይደል? ማለቴ አሁን ደላላ ሲባል ስሙንም ሰውዬውንም ማን ያምናል? እሱን እኮ ነው የምላችሁ። ታዲያ ፀሐይ ሰልችታው የ‘ቢቢሲ’ን ትንቢት ተስፋ ወደሚጠባበቀው ወዳጄ ስመለስ፣ ይኼው ወዳጄ አንድ ነገር አስታወሰኝ። እርሱም የአገራችን የሚዲያ ነፃነት ጉዳይ ነው። እያደር እያሸማቀቀን እያደር ይፋዊና ሕጋዊ የወንጀል አደባባይ እየሆነ መምጣቱን ሳስብ ሥጋቴ ያይላል።

ሲም ካርድ ከቴሌ ኔትወርክ ከእኛ?

ሰላም! ሰላም! ለመሆኑ ‹‹እየሄዳችሁ ነው?›› በማለት ብጠይቃችሁ አደናግራችሁ ይሆን? ለማንኛውም የሰማ ላልሰማ እንዲያሰማ የሰሞኑ የሰላምታ ፋሽን ይኼ መሆኑን ለመናገር እወዳለሁ።
ኑሮ በጠና ይዞን ጤና በጠፋበት ጊዜ ጤና ይስጥልኝ መባባል ከነትናንት ጋር እያለፈበት የሄደ ይመስላል። ጨዋታዬን ስጀምር ሁሌም በሰላምታ ነው። ከሰላምታውም ጋር ተያይዘው አንዳንድ ወጎችም ቁምነገሮች እንዳጫውታችሁ ይገፋፉኛል።

A Short History of Aircraft in Ethiopia

Ethiopia is becoming known for its signature airline which just announced its 63rd worldwide destination. Richard Pankhurst writes that even though airplanes took a long time to arrive


here a monoplane assembled in the country named Tsehai after Haile Selassie’s daughter was one of the first planes assembled in Africa.

The aeroplane was slow to make an appearance in Ethiopia, reportedly because Empress Zawditu and the Minister of War, Fitawrari Habte Giyorgis, were both conservative and opposed to the winged innovation.
The Ethiopian Government, reacting to Italian Fascist plans of conquest, decided, however, in 1929 to purchase a limited amount of aircraft. An order for two planes was despatched that year to a German firm, but delivery was delayed, it is said, by the French authorities in Jibuti, so that French aircraft could arrive in Ethiopia first.

ሃሎ ክቡር ሚኒስትር?

-    ሃሎ ክቡር ሚኒስትር?
-    እንዴት ነህ ደህና ነህ?
-    ወሩን ሙሉ’ኮ ተጠፋፋን፡፡
-    እንግዲህ መጀመርያ አራታችንም የየራሳችን ጉባዔ ስናካሂድ ነበር፡፡ ከዚያም የኢሕአዴግ ጉባዔ በባህር ዳር ተካሂዶ እዚህም እዚያም ስል አልተመቸኝም፡፡
-    በቃ አሁን አዲስ አበባ ስለመጡ እንገናኝና ያቺን ጉዳይ እንጨርሳት፡፡
-    እ - - - ?
-    ስልኩ አይሰማም ክቡር ሚኒስትር?
-    እ - - - ?
-    በቃ አይሰማም ክቡር ሚኒስትር - በአካል ቢሮዎ እመጣለሁ፡፡
-    አትምጣ ቆይ እኔ እደውልልሃለሁ፡፡
-    ጊዜ የለማ - ሰዎቹ ሁሉንም ነገር አዘጋጅተዋል፡፡ የት እናስገባው እያሉ ናቸው፡፡ ዛሬ እንጨርስ እያሉ ናቸው፡፡ ማታ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ፡፡ ዕድሉ እንዳያመልጥዎ ቢቀበሉዋቸው ጥሩ ነው፡፡ ካልናቸው እጥፍ ነው ያዘጋጁት፡፡ ያውም በውጭ ምንዛሪ፡፡
-    በቃ በቃ በስልክ አታውራ፡፡ ለምሳ እኔ ቤት እንገናኝ፡፡
-    እሺ - ቤት እመጣለሁ፡፡
[ቤት ተገናኙ ወሬ ቀጠሉ]