Monday, May 25, 2015

አስራ ሁለቱ አጋንንቶች ይዉረዱ



መጋቢት ፬ ቀን 1910 የሀገሬ ሰዉ የመንግስት ሹመኞች እንድወርዱለት ያቀረበዉ ጥያቀ በደጃዝማች ከበደ ተሰማ የታሪክ ማስታወሻ በተባለዉ መፅሐፋቸዉ የምከተለዉን ፅፈዋል።


ቃሉም ይህ ነዉ ጌታችን እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ዓለም ፈጥሮ 12 ሐዋርያትን አገር ከፍሎ እንድያስተምሩ ያሰማራቸዉ ለመምሰል ላገሩና ለመንግስቱ ልማት በእዉነት እንድመሰክሩና እንድሰሩ 12ቱን ሚንስትሮች ደጉ ጌታችን አፄ ምንልክ መርጠዉ ቢሾሟቸዉ ለአገር ልማት ለህዝብ አንድነት በመምከር ፋንታ አንዱ ላንዱ ለየራሳቸዉ ጥቅም በመመልከት አገሩን አበላሹት እንጂ ለመንግስት የጠቀሙትና የሰሩለት ጉዳይ የለም።
12ቱ ሐዋሪያት በማየት የተሾሙት ሚንስትሮች 12 አጋንንት ስለሆኑብን እንድሻሩ እንፈልጋለን፤ለምሳሌ የሥራ ሚንስተሩ ተብሎ የተሾመዉ የራሱን ቤት ለመስራትና በቤት ላይ ቤት እየቀጠለ ወደ ሰማይ ለመዉጣት ይገሰግሳል።እንድሁም የገቢ ሚንስተር የተባለዉ የራሱን ሃብት ብቻ በማደራጀቱ ምንልክ ቤት ለግብር የምሆን መሰናዶ ታጥቶ ባለፈዉ ሰሞን ከርሱ ቤት ዱቀት ተግዞ ተሰናዳ። ይህ ምን ያሳያል ሁሉም የየራሱን ጥቅም ለማደራጀት መዘጋጀቱን ነዉ፤

ደጃዝማች ከበደ ተሰማ
በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሰ የህይወት ታርክ በምለዉ መጽሐፍ
ዮሐንስ አድማሱ ጽፎት ዶ/ር ዮናስ አድማሱ እንዳቀናበረዉ
አ አ ዩ አሳትሞት ኻዮሉማ/xayouluma እንዳስነበባችሁ
ከገጽ ፳ የተቀነጨበ

ይህ ጥያቀ ዛረስ አያስፈልግም ?

No comments: