Wednesday, May 20, 2015

አወዛጋቢዉ የካምፓስ ምርጫ


ከሰፊዉ የእንቅልፍ ጊዜዬ መስዋዕት በመክፈል ከመኝታዬ ተነስቸ ወደ አዳራሽ ገባሁ። ባዳራሹ የምርጫ ቦርድ ተወካይ ተማሪዎችና የተወሰኑ የምርጫ እንግዶች በየወንበሩ ተሰካክተዋል፤ አብዛኞቹ ዉቃቢ የነገራቸዉ ይመስል በስፍራዉ ዝር አላሉም።እኔም የመጀመሪያዬ ስለነበር ጓጉቼ ከዝክ ቀደም እናት አባቴ የወሰዱትን የቅድሜ ምርጫ ስርዓቴ ሂደት ተከታትዬ አዉራ ጣቴን ለሰማያዊ ጂቢ አሰናድቸ ወንበር ሳብኩኝ።
የኮለጁ የምርጫ ቦርድ ተወካይ ተማሪ ስለምርጫ ብዙ ያወራል።ሌላዉ በዝምታና በግርምት ይሰማል።እኔም በዕለተ ሰንበቱ የምመርጠዉን ፓርቲ እያሰብኩ ተፎካካሪዎቹን እያነፃፀርኩ ነዉ፤ በኔ የምርጫ ክልል የምፎካከሩት አንድ ጠሚንስተር፣ አንድ አርሶ አደርና አንድ የባህል ሙዚቃ ቡድን መሪ ይፎካከራሉ። በነሱ የግል ብቃት ሳልገታ በፓርቲያቸዉ አቋምና አመለካከት የተወዳዳሪዎቹ ምስል እስክለጠፍ እየተጠባበኩ ነዉ።
የምርጫ ሁኔታዉ አዲስና ለገዥዉ ፓርቲ ግብዓት እንድሆን ከታሰቡት የምርጫ ክልሎች ዉስጥ የዩኒቬርሲስቲ የምርጫ ክልል፣ የታላላቅ ፕሮጀክቶች ምርጫ ክልልና ሌሎች አዳዲስ ኢህአዴጋዊ ታክትኮችንም አካቷል። ታድያላችሁ በዩኒቬርስቲ ደረጃ ባንድ ካምፓስ ብያንስ ፩ የምርጫ ጣቢያ ይኖራል ከበዛም በየ፯ መቶ ተማሪ ብዛት የተለያየ ጣብያ ይኖራል ተባልን ከዝያም ለጥቆ ለምሳሌ ያድሳባ ዩኒቬርስቲ 14 ቅርንጫፎችና ኮለጆች ስላሉት በየኮለጁና በየግቢዉ እንደየተማሪዉ ብዛት ይለያያል ተማሪ በብዛበት በ፮ ኪሎ ካምፓስ የምርጫ ጣቢያዎቹ እንደፌደራሉ ምርጫ ክልሎች የተከፋፈሉ ስሆኑ አነስተኛ ተማሪ ባለበት የምርጫ ጣቢያዉ እንደፌደራሉ የምርጫ ቦርድ ያስፈፅማል። ይህ ስተነተን ከላይ የጠቀስኳቸዉ ሶስቱ ዕጩዎች ሳይገለጹ ለፌደራሉ ም/ቤት የምወዳደሩ 25 ፓርቲዎች ስማቸዉ ይለጠፋል ከዝያ ባለፈ የእያንዳንዱ ምርጫ እጩዎች አይለጠፍም ማለት ነዉ።
ምኑ ነዉ ያወዛገበህ አትሉኝም
ያወዛገበኝማ በኛ የምርጭ ጣቢያ ተማሪዉ የፈለገዉን ፓርቲ ብመርጥ ዉጠቱ ወደ ዋናዉ ጣቢያ ክልል አይሄድም፤ ወደ ዋናዉ ጣቢያ የምሄደዉ የምርጫ ቦርዱ ራሱ አዲስ በምያዘጋጀዉ ቅፅ ላይ የተሞላዉ መረጃ ነዉ። ይህ ማለት በኔ አረዳድ ተማሪዉና የግቢዉ ማህበረሰብ የምጥለዉ ካርድ ለይሱሙላ ይቀመጣል(ለ ኤግዝብሽን ይሆናል እንዴምርጫ ጣቢያችን የቦርድ ተወካይ አገላለፅ)ስለዝክ ተማሪ የምጥለዉ ካርድ በና ግቢ ምርጫ ጣቢያ መሰረት ከዜሮ በታች ክብደት ያዘለ ወረቀት እንጅ ድምፅ አይደለም።
ይህች የምርጫ መላኛዉ ዉጥን ከተሳትፎ የዘለለ ምንም ፈይዳ የለዉም ማለት አትመስላች ሁም
ታዛቢዎቻችንም በስሜ ገለልተኛ በጎ መልዕክተኛ ማህበር ስም እየተቀያየሩ ይመጡብናል። ይመስገን በኛ ግቢ ግን ምንም አይታሰብም የምታዘበንና እዉነቱን የምገልጥልን የሰራዊ ጌታ የሰማዩ ንጉስ የሰማያዊ ርስት ባለቤት እግዝአብሄር ብቻ ነዉ።

ኻዮሉማ/xayouluma

No comments: