Showing posts with label ቅኝት. Show all posts
Showing posts with label ቅኝት. Show all posts

Sunday, November 15, 2015

ረሃብ ስንት ቀን ይፈጃል?




ረሃብ ቀጠሮ ይሰጣል?
ወይስ ቀን ቆጥሮ ይፈጃል?
"የሆድ ነገር ሆድ ይቆርጣል"
ያባላል ድሮም ይባላል
ይዘለዝላል ይከትፋል
ብቻ እስከምጨርስ ድረስ፤ ሆድ ለሆድ ጊዜ ይሰጣል

ወተት አንጀት ነጥፎ ሲላብ
ሆድቃ ደርቆ ሆድ ስራብ
ተሟጦ አንጀት ላንጀት ስሳብ...........
የጣር ቀጠሮ ስንት ነዉ
ለሰዉ ልጅ ሰዉ ለምንለዉ
ላይችል ሰጥቶት ለምያስችለዉ
ስንት ቀን ነዉ ? ስንት ለት ነዉ ?........
የማዕዱ ወዝ  ሳታጥጥ
አድባሩ አብዳ ሳትፈረጥጥ
ጥንብ ሳይተርፍ ሜዳ አይጥ
የቤት ድመት ሳታማምጥ
በእመቤቷ አስከሬን ብካይ
እሷም ዋይ ዋይ
ዉሻም በጌታ ስጋ ላይ
ቸነፈር በጣለዉ ስ ሳይ
አይ!...............
ስንት ቀን ትሁን የረሃብ አዋይ?.......
እስቲ እናንተ ተናገሩ፤ተርባችሁ የምታዉቁ
ከቸነፈር አምልጣችሁ፤ተርፋችሁ እንድሁ ሳታልቁ
ትንፋሽ ቀርቷችሁ እንድሆን፤ ያስችላችሁ እንደሆን ጥቂት
 ቀጠሮ ይሰጣል እልቂት?.
ስንት ምልዓት? ስንት ለሊት?
ጥንብ አንሳዉ ሳይወርድ በፊት፤ ሳይሞዠርጣችሁ ጥፍሩ
በጣረ ሞት አክናፋቱ፤አንዣቦ በመቅሰፍት እግሩ
አንደበት ተርፍዋችሁ እንድሁ ሳትነግሩ ከምትቀሩ
ካስቻላችሁ ተናገሩ።
ቆሽት ሲቃዉ ላያጣጥር፤ሰቀቀኑ ሳያጋግል
እስትንፋስ ስልምልም ሳትል
ቀጠሮ ይሰጣል ረሃብ ለስንት ቀን ለስንት ያህል
ስንት ስዓት ነዉ የረሃቡ አቅሙ?
ለ'ኔ ብጠማ ትርጉሙ
የሁለት ፊደል ድምጽ ነዉ ራብ የሚሉት ከነስሙ
እንጂ የ'ኔ ብጠዉማ
የት አዉቆት ጸባዩንማ
ብቻ ሲነገር ይሰማል
ይህን ሁለት ፊደል ቃል.............
ቃሉማ ያዉ በዘለማድ፤ ይነገራል ይለፈፋል
ይተረካል ይዘከራል
ይደጋግማል ይተቻል
እንጂ እንኳን ጠባዩን፤ የራብ ዕድሜዉን የት ያዉቃል..........
እና እምታዉቁት ንገሩን፤እዉነት ራብ ስንት ቀን ይፈጃል?..........
በጣር አፋፍ ላይ ያልህ ሰዉ፤ ራብ እንደት ነዉ እምያዛልቅ
ለስንት ቀን ቀን ይሰጣል፤አንደበትክን ላይሸመቅቅ
ሸረሪት በልሳንህ ላይ፤ የድር ትብትቡን ሳይሰራ
ቁራና ቀበሮ በቀን፤ ከቀየህ ድባብ ሳይደራ
ጥንብ አንሳ ልጭር ሳይመጣ፤ቅምቡርስ ከጎጆህ ጣራ
እንደፍካሬ ኢየሱስ ቃል፤ በጣር ምጽዓት ሳትጣራ
አንደበት ሳለህ ተናገር
የምታዉቅ የራብ ነገር
አስከረንክ ከየጥሻዉ፤ተርፎ እንድሁ ሳይቀረቀር
ስንት ደቂቅ ስንት ፋታ፤ ቀጠሮዉ ስንት ትንፋሽ ነበር
ቆሽት አርሮ ሳይፈረፈር
ትናጋህ በድርቀት ንዳድ፤ ጉሮሮህ ሳይሰነጠር?........
የሆድ ነገር ስንት ያቆያል
ቀጠሮ ይሰጣል እልቂት?.
ስንት ምልዓት? ስንት ለሊት?
ስንት ስዓት ነዉ ሰቆቃዉ፤ስንት ደቂቃ ነዉ ጭንቁ
እስቲ እናንተ ተናገሩ፤ተርባችሁ የምታዉቁ
ስንት ያቆያል ስንት ያዘልቃል?..........
እዉነት ራብ ስንት ቀን ይፈጃል?


ጸጋዬ ገብረ መድህን
 ጥር ፲፱፻፷፭
ዋልዲያ

ተርበዉ ለምያቁ ትሁንልኝ






Tuesday, June 2, 2015

መንግስት ግንቦት 16 ስራ ያስፈታቸዉን የኢትዮጵያ ህዝብ ካሳ ልከፍልለት ይገባል!


እሁድ ግንቦት 16/2007 ዓ/ም ላይ በመንግስት አዋጅና ንግርት መሰረት የተወደደዉ የሀገሬ ህዝብ ስራ ለፈታበት ካሳ ልከፈለዉ ይገባል።
ኻዮሉማ/xayouluma

ኑሮ የዝሆን ክብደት ያክል የተጫነበት ህዝቤ ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት በሰልፍ ያባከነዉን የትግል ጊዜዉን የቆመረበት መንግስት ይህን 40 ሚሊየን ህዝብ ልክሰዉ ይገባል።አሃ ምርጫ ቦርድ 38 ሚሊየን መራጮችን ነበር የመዘገበዉ፤ይሁና የምርጫ ታዛቢዉ፣አጨብጫቢዉ፣ተወዳዳሪዉ( እነ ዶ/ር መራራን ጨምሮ)እና ዳኛዉ ባጠቃላይ ሁለት ሚሊየን አይሞላም?
ከጉሊቲ እስከ ጉልበት ሰራተኛ፣ከታካሚ እስከ አካሚ፣ከገዢ እስከ ተገዢ፣ከደላላ እስከ ደሀስፖራ፣ ከስደተኝ(በሀገር ዉስጥ የተሰደዱት)እስከ አሳዳጅ እና ሌሎች ብዙ ብዙ ሚሊየን ህዝብ ከተፈፀመበት ክህደት ጋር የምስተካከል ባይሆንም ተገቢ ካሳ ልከፍለዉ ይገባል ባይ ነኝ። መብቴ መሰለኝ
ኑሮ ሱሪ ባንገት ለሆነበት ዜጋ ካርድ ካልጣልክልኝ ወየዉልህ የተባለዉ ወገን በቴሌቪዥን፣በሬድዮ፣በጋዜጣ እና በየሞባይሉ የተደረጉ ቅስቀሳዎች ለኑሮ ግብዓታችን የጠብታ ያህል ባይጨምርም ለመምረጥ ተገደናል።ተወዳዳሪዎቹስ ብሆኑ ራሳቸዉንም የካዱ ባስመስለዉ ዉድድር የህዝብ ድምፅን እንደ አየር ሁኔታ የተተነበየዉ ፭ኛ ዙር ምርጫ በሰላም ተጠናቋል። የምገርመዉ ነገር  አወዳዳሪዉ፣ተወዳዳሪዉ፣ታዛቢዉና አሸናፊዉ ፓርቲ ለዉድድሩ ድምቀት የተጠቀማቸዉ ኢትዮጵያን ለራሳቸዉ እንኳን ከኢህአዴግ በላይ ቦታ የሌላቸዉ በማስመሰል የለጠፋቸዉ ዉጠቶች አስገርሞኛል።

Monday, May 25, 2015

ይድረስ ለኢትዮጵያ............

ዲዮጋን

ሰዉ ፍለጋ ከቤት ወጥቶ
እጅግ ብዙ ተንከራቶ
ተመለሰ ከቤቱ
ሰዉ ጠፍቶ ባገሪቱ።
                አዘርግ(2003 e.c)

ሌቱን ሙሉ ኣሰብኩ፣በጣም አሰብኩ፣ በመጨረሻም፣ከቤቴ ወጣሁ፣አዲስ አበባን በእግሬ እየኳተንኩ ቃኘዉ  አእምሮዬ ላይ የጥያቄ ክምር ተከማችቷል።መጠየቅ የምፈልገዉ ደግሞ ኢትዮጵያን ነዉ እናም ጀመርኩ.............

እኔማ ሰምቸ ነበር ይህች ኢትዮጵያ የምትባል ምድር እንኳን ለህዝቦችዋ በግዛትዋ የሚያልፍ አዉሮፕላኖች ይባረካሉ!

እኔማ ሰምቸ ነበር ዓለም ባንድ መሪ የምትመራበት ዘመን ይመጣል ! ያኔ በዓለም ላይ የበዛ ሰላም፣ የበዛ ጤና፣ የበዛ መተሳሰብ፣ የበዛ ፍቅር፣የበዛ አንድነት ይሆናል ጦርነት ፣ጥል ፣ጥላቻ ፣ዘረኝነት ፣ርሀብ ምቀኝነት ፣መነቋቆር  ይወገዳል!  ያ መሪ ደግሞ ከኢትዮጵያ ነዉ!

አስራ ሁለቱ አጋንንቶች ይዉረዱ



መጋቢት ፬ ቀን 1910 የሀገሬ ሰዉ የመንግስት ሹመኞች እንድወርዱለት ያቀረበዉ ጥያቀ በደጃዝማች ከበደ ተሰማ የታሪክ ማስታወሻ በተባለዉ መፅሐፋቸዉ የምከተለዉን ፅፈዋል።


ቃሉም ይህ ነዉ ጌታችን እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ዓለም ፈጥሮ 12 ሐዋርያትን አገር ከፍሎ እንድያስተምሩ ያሰማራቸዉ ለመምሰል ላገሩና ለመንግስቱ ልማት በእዉነት እንድመሰክሩና እንድሰሩ 12ቱን ሚንስትሮች ደጉ ጌታችን አፄ ምንልክ መርጠዉ ቢሾሟቸዉ ለአገር ልማት ለህዝብ አንድነት በመምከር ፋንታ አንዱ ላንዱ ለየራሳቸዉ ጥቅም በመመልከት አገሩን አበላሹት እንጂ ለመንግስት የጠቀሙትና የሰሩለት ጉዳይ የለም።
12ቱ ሐዋሪያት በማየት የተሾሙት ሚንስትሮች 12 አጋንንት ስለሆኑብን እንድሻሩ እንፈልጋለን፤ለምሳሌ የሥራ ሚንስተሩ ተብሎ የተሾመዉ የራሱን ቤት ለመስራትና በቤት ላይ ቤት እየቀጠለ ወደ ሰማይ ለመዉጣት ይገሰግሳል።እንድሁም የገቢ ሚንስተር የተባለዉ የራሱን ሃብት ብቻ በማደራጀቱ ምንልክ ቤት ለግብር የምሆን መሰናዶ ታጥቶ ባለፈዉ ሰሞን ከርሱ ቤት ዱቀት ተግዞ ተሰናዳ። ይህ ምን ያሳያል ሁሉም የየራሱን ጥቅም ለማደራጀት መዘጋጀቱን ነዉ፤

ደጃዝማች ከበደ ተሰማ
በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሰ የህይወት ታርክ በምለዉ መጽሐፍ
ዮሐንስ አድማሱ ጽፎት ዶ/ር ዮናስ አድማሱ እንዳቀናበረዉ
አ አ ዩ አሳትሞት ኻዮሉማ/xayouluma እንዳስነበባችሁ
ከገጽ ፳ የተቀነጨበ

ይህ ጥያቀ ዛረስ አያስፈልግም ?

Thursday, May 21, 2015

መንግስት ያሰራቸዉ ኔትዎርኮች ይፈቱልን ?





"ለብሔራዊ ደህንነት ስባል መራጩ የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫ እስክያልፍና ዉጠቱ እስክነገር ቡና እንዳይጠጣ።"
                   ኢፌዴሪ መንግስት

"አንዳንድ አልቧልተኞች ባልተፈቀደላቸዉ ቡና ቤቶች የሽብር ወሬን ስለምነዙና ሰላማዊዉን ህዝብ ስለምያሸብሩ የመንግስት ዉሳኔ ፓርቲያችን ተገቢ ነዉ ስል አምኖ በመቀበል እንደፓርቲ ተግብሯል።"
                 የኢህአዴግ አፌ ቀላጠ ሬድዋን ሁሴን

"መንግስት በህብረተሰቡ ላይ እያደረገ ያለዉ አምባገነናዊ ተፅዕኖ ፫ ሺ ዓመት ቡና የመጠጣት ባህላችን አያስቀረዉም።"
                   ኢንዢነር ይልቃል ጌትነት

"ኢህአዴግ ሰፊዉ ህዝብ ስለምርጫ መረጃ እንዳይለዋወጥ የወሰደዉ እርምጃ አግባብነት የጎደለዉ ቢሆንም የመንግስትን ዉሳኔ እንደፓርቲ በፀጋ ተቀብለናል።"
                 የቅንዥቱ አየለ ጫሚሶ

"ወያኔ አፋኝ ስርዓቱን ስር በሰደደ ህዝባዊ ጥላቻ ላይ በማድረግ በነፃነት የመናገር፣የመወያየትና ጎረበት ጠራርቶ ቡና የመጠጣትና የማማት ሰብዓዊ መብቱን የምጥሰዉን ልያቆም ይገባል።"
               የጉንቦት ፯ቱ ነጋ ብርሃኑ

"የኦሮሞ ህዝብና ሌላዉ የሃገርቱ ህዝብ ቡና ከጂማ ከተገኘበት ጊዘ ጀምሮ 'kotta buna dhuuge 'እየተባባለ ዛሬ የደረሰበትን ቡና በዘመናዊ መልክ የማፍላትና የመጠጣት መብቱ ለቦለቲካ ግብዓትነት በማሰብ ማቆም የለበትም።"
                  ዶር መራራ ጉዲና( ገነትን ያለማዕረገ አትጥርኝ ነበር ያላት)

Wednesday, May 20, 2015

የሰማያዊ ነገር


ልጅ ሆኘ ህፃን ሳለሁ የዓመት በዓል በመጣ ቁጥር ካባቴ ጋር ሙግት ገጥማለሁ። የሙግቴ መነሻ የኔ ምርጫና ያባቴ ምርጫ ነበር። አባቴ በተፈጥሮዉ ድያብሎስ ስመርቀዉ የኔን ምርጫ ይጠላል። በየእንቁጣጣሹ ሰማያዊ ፋንት በ፲ ብር፣ሰማያዊ ካልሲ በ ፲ብር፣ ሰማያዊ ጫማ በ፶ ብር፣ ሰማያዊ ሱሪ 45 ብር ፣ ሰማያዊ ሸሚዝ በ37 ብር ፣ ሰማያዊ መነፅር በ 12 ብር፣ ሰማያዊ ኮፊያ በ22 ብር፣ ሰማያዊ ሻማ በ ፶ ሳንቲም፣ ሰማያዊ ፊኛ እና ት/ቤት ስሄድ ከፀሃይና ከሰቆቃ የምታደገኝን ሰማያዊ ዣንጥላ በ17 ብር ይገዛልኝ ነበር።

ጥሎበት ያባቴ ምርጫ ሰማያዊ ባይሆንም ከብጫና መሰሎቹ ይሻለኛል ብየ ነበር የምያለቅሰዉ። አድገም ት/ት ስጀምር በት/ቤት ዉስጥ ከሰማያዊ እስክሪብቶ ሌላ ተጠቅሜ አላዉቅም።መምህራችን

"ኻዮሉማ/xayouluma ላንዳንድ ጠቃሚ ማስታወሻዎች ቀይ እስክሪብቶ ተጠቅም "

ብለኝም እኔም እንደ ሪዮት ዓለም ቀይ እስክሪብቶ ፈራለሁ።

Monday, March 31, 2014

ለኔትዎርኩና ለመብራቱ መጥፋት “አዋቂ” ጋ ብንሄድ ይሻላል!!

  • Written by  ኤልያስ 


  • ጐዳና የሚያፀዳ መኪና በማስመጣት ከአፍሪካ ቀዳሚ አይደለንም
  • ካሜሩን ከ11 ዓመት በፊት አስመጥቻለሁ ብላለች
  • ታንዛንያ ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ነኝ ባይ ናት
      እናንተ… ያ የማሌዥያ (እየበረረ የጠፋ) አውሮፕላን እስካሁን እኮ አልተገኘም፡፡ እኔ የምለው---የዓለም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሁኔታ ጥርጣሬ አልፈጠረባችሁም? አንዴ ቻይና ትነሳና በሳተላይት ሦስት የአውሮፕላን ስብርባሪም ባህር ውስጥ ወድቆ አይቻለሁ…ትላለች፡፡ (እስካሁን አንዲትም ስባሪ አልተገኘም!) ቬትናምም እንዲሁ አንዳች ነገር ያየሁ ይመስለኛል ብላለች (ቅዥት ነው እንዴ?) አሁን ደግሞ አውስትራሊያ አካባቢ በሳተላይት ስብርባሪ እንደታየ ተሰምቷል፡፡ ነገርየው እኮ ግራ ያጋባል። የአውሮፕላኑ ባለቤት የማሌዥያ መንግስትም በሳይንስና ቴክኖሎጂው ግራ ቢገባው ጠንቋይ ጋ ሄዶ ስለአውሮፕላኑ ጠየቀ ተብሏል፡፡ (ከሳተላይት ጠንቋይ ይሻለኛል ማለት እኮ ነው!)

የማሕበረ ቅዱሳን የመጨረሻዎቹ ቀናት – ከተመስገን ደሳለኝ


                   
በኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የሚመራው መንግስት ከናቅፋ እስከ ጉና ተራራ ያሉ ምሽጎቻቸውን ከሰማይ በጦር አይሮፕላን፣ ከምድር እሳት በሚያዘንቡ ቢ.ኤሞችና መድፎች ሳያቋርጥ ደበድብም፤ በሀገሪቱ ሰሜናዊ አካባቢ ከቀን ወደ ቀን ግዛታቸውን እያሰፉ የተጠናከሩት ‹‹ወንበዴዎች›› ራስ ምታት ሆነውበታል፡፡ የኤርትራ ‹‹ነጻ አውጪ›› ቤዝ-አምባው በተወሰነ መልኩም ቢሆን ለጥቃት የመጋለጥ እድሉ አናሳ በሆነው የሳህል በረሃ በመሆኑ አብዛኛው የአመራር አባል መሸሸጊያው አድርጎታል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ በትግራይ አካባቢ የሚንቀሳቀሱት የወያኔ መሪዎች ምሽጋቸው እንደ ሳህል ምቹ ባለመሆኑ፤ በርካታ ክፉ ቀናትን ያሳለፉት በተራራማ አካባቢዎች በሚገኙ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ገዳማት ውስጥ ተደብቀው እንደሆነና ከቦታ ቦታ መዘዋወር ሲፈልጉም የመነኮሳቱን አልባሳት ይጠቀሙ እንደነበረ በትግሉ ዙሪያ የተዘጋጁ ድርሳናት ያወሳሉ፡፡ በተለይም ታጋይ መለስ ዜናዊ፣

የፍትሕ ሚኒስቴር ታሪካዊ ዳራ

ፍትሕ ሚኒስቴር አሁን ያለውን ስያሜ ከመያዙ በፊት የተለያዩ መጠሪያዎችን በመያዝ አወቃቀሩም ሆነ አደረጃጀቱ በየጊዜው ለውጦች ሲካሄዱበት መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት የሚኖረው አደረጃጀት ያለፈባቸውን ሥርዓተ ማህበራትና ቅርፀ መንግስታት አሠራርና ይዘት በሚያንፀባርቅ መልኩ የተደራጀ ሲሆን ይህም በተለይ ከዳኝነት ሥርዓቱ ጋር እስከ ቅርብ ጊዜያት የነበረው ቁርኝት ለዚህ አመላካች ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
ስለሆነም ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርነው ሁሉ ይህ ፅሁፍ የፍትሕ ሚኒስቴር ከየት ተነስቶ አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ ሊደርስ እንደቻለ፣በየወቅቱ ሲከተላቸው  የነበሩ አሠራሮች ምን እንደሆኑ፣እንዲሁም አሁን ያለው አወቃቀርና የደረሰበት ደረጃ  ከዚህ ቀጥሎ ለማየት እንሞክራለን፡፡
ሀ. ፍትሕ ሚኒስቴር እስከ ደርግ ውድቀት

Tuesday, March 4, 2014

የአርሲ ጉዞዬ አስደናቂ ማስታወሻ 2

 

 Written by  ነቢይ መኮንን 

 

 የአርሲ ጉዞዬ አስደናቂ ማስታወሻ
(ካለፈው የቀጠለ)
ከ38 ዓመት በኋላ አስከሬናቸው የተገኘው የፊዚክስ ባለሙያው የዶክተር ሙሉጌታ በቀለ አባት የፊታውራሪ በቀለ ኦገቶ አስደማሚ የአስከሬን ማሳረፍ ሥነ ስርዓት በሳጉሬ ወረዳ/አርሲ/
የጉዳዩ ጭብጥ፤
ፊታውራሪ በቀለ ኦገቶ በደርግ መንግስት ከሌሎች 16 ወዳጆቻቸውና ዘመዶቻቸው ጋር በግፍ ተገድለው አስከሬናቸው ዘመድ ወዳጅ እንዳያውቅ፣ እንዳያገኝ ተደርጎ፤ በደርግ መንግስት አረመኔነት፤ የተጣሉበት ሳይታወቅ ለ38 ዓመታት ቆይቷል፡፡
ይሁን እንጂ በልጆቻቸው በተለይም በዶ/ር ሙሉጌታ በቀለ ጥንካሬና ፅናት፤ የተሞላበት የረጅም ጊዜ ፍለጋ፤ ታህሳስ 17/2006 ዓ.ም በአሰላ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አፅማቸው ተቆፍሮ ተገኝቷል፡፡
ሁኔታው ለዘመድ ወዳጆቻቸው፣ ለአገር ሽማግሌዎችና አብረዋቸው ለተሰዉ ሰማእታት ቤተሰቦች ታህሳስ 28/2006 ዓ.ም ይፋ ተደረገ፡፡
አፅሙን በክብር ለማሳረፍ በዘመዶቻቸው፤ በወዳጆቻቸው፣ በሰማእታቱ

Thursday, February 27, 2014

የአርሲ ጉዞዬ አስደናቂ ማስታወሻ

                                                                                              Written by  ነቢይ መኮንን

 ከ38 ዓመት በኋላ ከመቃብር የወጣው አስከሬን ትርዒት

የፊዚክስ ባለሙያው የዶ/ር ሙሉጌታ በቀለ አባት የፊታውራሪ በቀለ ኦገቶ አስከሬን እንዴት ተገኘ? ዝርዝሩ ብዙ ነው፤ ጉዳዩ ግን ተዓምር ተባለ!

ወደ አርሲ አሰላ - ሳጉሬ መንገድ የጀመርነው ቅዳሜ የካቲት 8 ቀን 2006 ዓ.ም ከንጋቱ ለአንድ ሩብ ጉዳይ ነው፡፡
ከናዝሬት .. ወደ ሶደሬ አቅጣጫ … መልካሰዲ ስንደርስ ወደ ቀኝ ዞረን ዴራ፣ ኢቲያን አልፈን በብቅል ፋብሪካ አድርገን አሰላ ገባን፡፡ ከዚያ ወዲያ እንግዲህ ከ 23 ኪ.ሜ በኋላ ሳጉሬ ወረዳ ልንሄድ ነው፡፡
ወደ ሳጉሬ ከመሄዳችን በፊት ወደ አሰላ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን መሄድ ዋንኛው የመርሀ-ግብሩ መነሻ ነው፡፡ ለምን? ታሪኩ እዚህ ጋ ይጀምራላ፡፡
38 ዓመት የፈጀው አስከሬን ለምን ይሄን ያህል ጊዜ ፈጀ? ሂደቱ ምን ይመስላል? ከመጨረሻው ትርዒት ጀምረን ወደ ኋላ 38 ዓመት እንጓዛለን፡፡

Saturday, September 28, 2013

ሙዝ!

የግል ሐኪምዎ የሆነው ሙዝ!
በስትሮክ የመሞት አደጋን ከ50-60 በመቶ ለመቀነስ ያስችላል
ለስኳር ህመምና ለደም ማነስ ሙዝን መመገብ ይመከራል
በኢትዮጵያ እንደተገኘ የሚነገርለትና በዓለማችን በስፋት እየተመረተ ለምግብነት የሚውለው ሙዝ እጅግ በርካታ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ ሙዝ ከምግብ ይዘቱ በተጨማሪ ለተለያዩ በሽታዎች ፈውስ ሊያስገኙ የሚችሉ ንጥረ ነገሮችንም አካቶ ይዟል። እነዚህ ንጥረነገሮች ለበርካታ በሽታዎች ፈውስ ከመሆናቸውም በላይ፣ በሽታው ከመከሰቱም በፊት ለመከላከል የሚያስችለንን አቅም ያጐናጽፉናል፡፡ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በጠቅላላ ህክምና ክፍል ሐኪም የሆኑት ዶ/ር ታዬ አለማየሁ እንደሚናገሩት፤ ሙዝ በስትሮክ ምክንያት ሊከሰት የሚችለውን ሞት በግማሽ መቀነስ ይችላል፡፡

Tuesday, April 16, 2013

የመታሰቢያ ድርጅቶች (ፋውንዴሽን) ከአፄ ምኒልክ እስከ መለስ

 የመታሰቢያ እና በጐ አድራጐት ድርጅቶች የ85 ዓመታት ጉዞ
ከመላው ዓለም በፊዚክስና ኬሚስትሪ፣ በሕክምናና በሥነ ፅሁፍ እንዲሁም በሰላም ዙርያ የላቀ አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰዎች ተመርጠው የሚሸለሙበት የኖቤል በጐ አድራጐት ድርጅት በተመሰረተ በ10ኛ ዓመቱ በኢትዮጵያም ተቀራራቢ ዓላማ ያለው “መታሰቢያ ድርጅት” ተቋቁሟል፡፡ አፄ ምኒልክ ከሞቱ ከአራት ዓመት በኋላ ልጃቸው ንግሥት ዘውዲቱ በ1910 ዓ.ም ለአባታቸው መታሰቢያነት አራት ኪሎ የሚገኘውን የበአታ ለማርያም ገዳም ቤተክርስቲያንን ማሰራት ጀመሩ፡፡
በግዛው ኃይለማርያም ተዘጋጅቶ የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ድርጅት በ1956 ዓ.ም ባሳተመው “ዳግማዊ ምኒልክ” የተሰኘ መፅሃፍ፤ የበጐ አድራጐት ሥራዎች በሦስት ዘርፎች ተከፍለው እንደሚከናወኑ ያመለክታል፡፡ የመጀመሪያው መታሰቢያቱን ማዕከል ያደረገው ነው፡፡ ግንባታው በተጀመረ በአስረኛ ዓመቱ በ1920 ዓ.ም የተጠናቀቀው የበአታ ለማርያም ገዳም ቤተክርስቲያን፤ የአፄ ምኒልክ፣ የእቴጌ ጣይቱ፣ የንግሥት ዘውዲቱ፣ የብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ የልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ አስከሬንና የተለያዩ ታሪካዊ ቅርሶች መቀመጫ ሆኗል፡፡ መታሰቢያ ድርጅቱ፤ በሁለተኛ ደረጃ ተግባራዊ ያደረገው መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ማቋቋም ሲሆን በ1925 ዓ.ም የተመሰረተው የአብነት ትምህርት ቤት፤ አገልግሎቱን ሳያቋርጥ እስካሁን በመቀጠል 80 ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡

ያልተጠናው የኢትዮጵያውያን ፍልስፍና

ሀገራችን ኢትዮጵያ ገና ያልተጠኑ የበርካታ ጥንታዊ ሥነጽሁፎች ባለቤት ናት፤ ማጥናት አቅቶን ሌሎች አጥንተው የቅጂ መብቱን ከመውሰዳቸውና የታሪክ ክፍትት ተፈጥሮ በመጪው ትውልድ ተወቃሾች ከመሆናችን በፊት የዘርፉ ምሁራን ጥናትና ምርምር በማካሄድ፣ ዩኒቨርስቲዎች ጉዳዩን የምርምር አቅጣጫቸው ውስጥ በማስገባት፣ ዜጎችም ጥንታዊ የጽሁፍ ሃብታችንን አስፈላጊነት ተገንዝበን ከዘራፊዎች በመጠበቅ ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል፡፡ ኢትዮጵያ ዘመናትን ያስቆጠሩ ሥነቃላዊና የጽሁፍ ፍልስፍናዎች ባለቤት ናት፡፡ ከአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች በተለየ መልኩ በርከት ያሉ የፍልስፍና ስራዎችን በመስራት በቀዳሚነት የምትጠቀሰው ኢትዮጵያ፤ በጥንታዊው የግእዝ ቋንቋ ከተጻፉት የፍልስፍና ስራዎቿ መካከል ከፊሎቹን በትውልድ ካናዳዊ፣ በምርጫ ደግሞ ኢትዮጵያዊ የሆነው ፕሮፌሰር ክላውድ ሰምነር ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ በመተርጎም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቁ ሲያደርግ፤ ሌሎች በርካታ በግዕዝና በአረብኛ ቋንቋዎች የተጻፉ የጽሁፍ ስራዎች በጥንታዊ ቤተእምነቶችና ቤተመዛግብት ውስጥ ተቀምጠው ክላውድ ሰምነርን የመሰሉ ፈላስፎችንና የጥንታዊ ጽሁፎች ተመራማሪዎችን (philologists) እይታ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

Wednesday, April 3, 2013

የኣበሾች ሁሉ የኩራት ምንጭ






የኣበሾች ሁሉ የኩራት ምንጭ
የኣክሱም ስርወ መንግስት በኣፍሪቃ ሰሜናዊ ምስራቅ የሚገኝ እጀግ ጠቃሚ የንግድ ብሔር ነበር፡ ፡ ስርወ መንግስቱ በ300 ዓ.ዓ. ኣከባቢ ኣብቦ በ 300 ዓ.ም. ኣከባቢ ከፍተኛ የስልጣኔ ድረጃ የደረሰ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡ ከሮማ ስርወ መንግስትና ከጥንታዊዋ ሕንድ ጋር የንግድ ግንኝነት የነበረው ስርወ መንግስት የራሱ የመገበያያ ገንዘብ ነበረው፡ ፡ የኣክሱም ስርወ መንግስት በደቡባዊ የኩሽ ግዛት ላይ የበላይነትን ይዞ የቆየ ከመሆኑም በላይ የኣረቡን የባሕር ሰላጤ በከፊል በፖሊቲካ መቆጣጠር የቻለ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡
የኣክሱም ስርወ መንግስት በኣፍሪቃ ሰሜናዊ ምስራቅ የሚገኝ እጀግ ጠቃሚ የንግድ ብሔር ነበር፡ ፡ ስርወ መንግስቱ በ300 ዓ.ዓ. ኣከባቢ ኣብቦ በ 300 ዓ.ም. ኣከባቢ ከፍተኛ የስልጣኔ ድረጃ የደረሰ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡ ከሮማ ስርወ መንግስትና ከጥንታዊዋ ሕንድ ጋር የንግድ ግንኝነት የነበረው ስርወ መንግስት የራሱ የመገበያያ ገንዘብ ነበረው፡ ፡ የኣክሱም ስርወ መንግስት በደቡባዊ የኩሽ ግዛት ላይ የበላይነትን ይዞ የቆየ ከመሆኑም በላይ የኣረቡን የባሕር ሰላጤ በከፊል በፖሊቲካ መቆጣጠር የቻለ ስርወ መንግስት ነበር፡ ፡

Monday, April 1, 2013

ይሓ

በቅድመ አክሱም ታሪክ የይሓን ሥልጣኔ በ100 ዓመት ወደፊት የሚያስቀድም 2 ሺሕ 800 ዓመት ዕድሜ ያለው ጥንታዊ ሕንፃ በቁፋሮ መገኘትን ያበሰሩት ኢትዮጵያውያንና ጀርመናውያን ባለሙያዎች ናቸው፡፡ ያገኙትም በይሓ አካባቢ ግራት በዓል ግብሪ በተሰኘ ስፍራ ነው፡፡ እንደተመራማሪዎቹ ግኝቱ በኢትዮጵያና በየመን መካከል ቀድሞ በነበረ ግንኙነት  የሚናገሩ መላምቶችን የሚቀይርና የኢትዮጵያን ታሪክ የሚያድስ ይሆናል፡፡

ከአክሱም ሰሜን ምሥራቅ አቅጣጫ 56 ኪሜ ርቆ የሚገኘው ይሓ ከጥንታዊው የአክሱም ሥርወ መንግሥት በፊት የነበረው የደአማት ሥርወ መንግሥት መቀመጫ እንደነበረ ይነገራል፡፡ በሌላ በኩል በይሓ አሁንም ድረስ ፍራሹ ቆሞ የሚታየው ምኩራብ አለ፡፡ ምኩራቡ ‹‹አልሙቃህ›› ለተባለ የጨረቃ አምላክ አምልኮት ይፈጸምበት እንደነበረ በጥናት ተረጋግጧል፡፡

የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ኤጀንሲ አንድ ሕትመት እንዳሳየው፣ ይሓ የጥንታዊው የደኣማት መንግሥት መቀመጫ ማዕከል ሆኖ ያገለገለ ሲሆን፣ መንግሥቱም ከክርስቶስ ልደት በፊት ከስምንተኛ እስከ ሦስተኛ ክፍለ ዘመን እንደቆየ ጥናቶች ያወሳሉ፡፡ ይሓ በወቅቱ የንግድ፣ የእርሻ፣ የሥነጥበብና የአስተዳደር ማዕከል ሆኖ በማገልገሉ በላቀ ደረጃ ላይ ደርሶ እንደነበር የሚያሳዩ አሻራዎች እስካሁን ይታያሉ፡፡

A Short History of Aircraft in Ethiopia

Ethiopia is becoming known for its signature airline which just announced its 63rd worldwide destination. Richard Pankhurst writes that even though airplanes took a long time to arrive


here a monoplane assembled in the country named Tsehai after Haile Selassie’s daughter was one of the first planes assembled in Africa.

The aeroplane was slow to make an appearance in Ethiopia, reportedly because Empress Zawditu and the Minister of War, Fitawrari Habte Giyorgis, were both conservative and opposed to the winged innovation.
The Ethiopian Government, reacting to Italian Fascist plans of conquest, decided, however, in 1929 to purchase a limited amount of aircraft. An order for two planes was despatched that year to a German firm, but delivery was delayed, it is said, by the French authorities in Jibuti, so that French aircraft could arrive in Ethiopia first.

Friday, March 29, 2013

የኢንተርኔት ስለላና ቅኝት

ዘመኑ የኢንተርኔት ብሎም የመረጃ ተብሎ ቢነገርለትም በኢንተርኔት የተሰራጩ መረጃዎችን ለማገድ እርምጃ የሚወስዱ አካላት መበራከታቸዉ ይታያል። በኢንተርኔት ላይ ጥብቅ ቁጥጥርና ስለላ የሚያካሂዱ ሀገሮችን ዝርዝር ይፋ ያደረገዉ ዘገባ ቁጥጥር የሚያደርጉ መንግስታትን ብቻ ሳይሆን ለእነሱ ቴክኒዎሎጂዉን የሚያቀርቡ ኩባንያዎችንም ማንነት አጋልጧል።

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት RSF በያዝነዉ ሳምንት ባወጣዉ የኢንተርኔት ቁጥጥርን የሚመለከት ዘገባ አምስት ሀገሮችን የኢንተርኔት ጠላት ሲል ፈርጇል። የሶርያ፤ ቻይና፤ ኢራን፤ ባህሬን እንዲሁም የቬትናም መንግስታት የኢንተርኔት መረጃዎችን ለመቆጣጠር ከሚሰነዝሩት የድረገፅ ጥቃት በተጨማሪ ዜጎችን ለመሰለል የግለሰቦችን የኢሜል መረጃ የሚያጠምዱ ፕሮግራሞችን በመጠቀም ግንባር ቀደም ተብለዋል። ከበርካታ ሀገሮች እነዚህ አምስቱ የተመረጡትም ለኢንተርኔት ቁጥጥሩ የሚጠቀሙበት ቴክኒዎሊጂ መራቀቅና በዚህ ስለላ መሠረትም ጋዜጠኞችና ዜጎቻቸዉን በማሰራቸዉ እንደሆነ የRSF የዘመናዊ መገናኛ ብዙሃን ዘርፍ ተመራማሪ ግሬግዋ ፑዤ ገልፀዋል።
በተለይም ቻይና የኤሌክትሮኒክ መከላከያዋ ከዓለም ምናልባትም የረቀቀ ተብሎ ሲገመት ይህንኑ ቁጥጥሯን ለማጠናከር የግል ኢንተርኔት ኩባንያዎች ዜጎቿን ለመሰለል የሚረዱ ስልቶችን

የናይጀርያ የነዳጅ ዘይት


ናይጀርያ ያለ ነዳጅ ዘይትዋ ምንም ነገርን ማንቀሳቀስን አትችልም። 80 በመቶዉ የሀገሪቱ ገቢ የሚገኘዉ ከዚሁ ከነዳጅ ዘይት ነዉ። ናይጀርያ የነዳጅ ዘይትዋን ከምድረ-ከርስ ማዉጣት ከጀመረችበት ከጎርጎረሳዉያኑ 1958 ዓ,ም ጀምሮ በከፍተኛ የነዳጅ ምርት አቅርቦት ከዓለም ስምንተኛ ደረጃን ይዛ ትገኛለች።
ይህ የነዳጅ ምርት በኒጀር ዴልታ ለሚኖሩ ህዝቦች ያስገኘላቸዉ አንዳችም ጥቅም የለም። በአንጻሩ በነዳጅ ምርቱ ሰበብ ህዝቦችዋ በተበከለ አካባቢ ላይ እንዲኖሩ መርዛማ ጋዝ አየርን በየቀኑ እንዲተነፍሱ ዳርጎቸዋል።
ቦዶ በሚሰኘዉ ወደብ ላይ አንድ አነስተኛ የሞተር ጀልባ ቆሞዋል። ቦዶ በኒጀር ዴልታ ደለል ላይ ከሚገኙት በርካታ መንደሮች እንዷ ናት። ደቡባዊ ምስራቅ ናይጀርያን ወጣ ብለዉ የሚገኙ ማህበረሰቦች ጀልባ እና አነስተኛ ታንኳ እጅግ አስፈላጊ የመጓጓዣ መሳርያቸዉ ነዉ።
አሳ ማስገርም ለምዕተ አመታት የኖረ ዋናዉ የገቢ ምንጫቸዉ ነዉ። በጎርጎረሳዉያኑ 2008 ዓ,ም መፀዉ ወራት ላይ በቦዶ ያለዉ ሁኔታ ከመቅስበት ተቀይሮአል። ይኸዉም ሼል ከተሰኘ የነዳጅ ማዉጫ ድርጅት የተዘረጋዉ የነዳጅ ዘይት ቧንቧ ተቀዶ የፈሰሰዉ ዘይት ከአንድ ሳምንት በላይ አካባቢዉን እና ዉሃን በክሎአል። የዚህ አደጋ ጠባሳ ከአራት አመት በኋላ ዛሪም አካባቢዉ ላይ በጉልህ ይታያል።

Wednesday, March 20, 2013

National Bank of Ethiopia

The National Bank of Ethiopia was established in 1963 by proclamation 206 of 1963 and began operation in January 1964. Prior to this proclamation, the Bank used to carry out dual activities, i.e. commercial banking and central banking. The proclamation raised the Bank's capital to Ethiopian dollars 10.0 million and granted broad administrative autonomy and juridical personality. Following the proclamation the National Bank of Ethiopia was entrusted with the following responsibilities.
» To regulate the supply, availability and cost of money and credit.
» To manage and administer the country's international reserves.
» To license and supervise banks and hold commercial banks reserves and lend money to them.
» To supervise loans of commercial banks and regulate interest rates.
» To issue paper money and coins.
» To act as an agent of the Government.
» To fix and control the foreign exchange rates.

However, monetary and banking proclamation No. 99 of 1976 came into force on September 1976 to shape the Bank's role