
"ተዉ የጀማል አባት እንዳይቆጭዎት ምልክትዎን ንብ ላይ ብያደርጉ ይሻሎታል!"
"ቆንጂዬ ምንነካሽ! ስያዩሽ እንድህ አትመስይም አንቺም ክህደት ትፈፅምያለሽ?"
"ማዘር አንድ X ያድርጉ ንቡን ልቆራርጡት ነዉ ያሰቡት? ምነዉ እርሶ ትልቅ ሰዉ አይደሉም ? አንደት አንድ ንብ ላይ ሶስት X ያኖራሉ ?"
ኻዮሉማ/xayouluma
"ከፊፋ በቀሰምነዉ የጎል ቴክኖሎጂ ምርጫዉን ታዝበናል።"
"እኔም ኮኒስ ዉስጥ ሆኘ የመታዘብ ተልዕኮዬን ተወጥቻለሁ።"
ዛሬ በሰፈራችን ሀይለኛ ጉድ የተባለለት ግጥሚያ ተስተናግዷል።ቅልጥ ያሌ ጫወታ ነበር ከኛ ቡድን
ግርግር፣
በቃኝ፣
ካሊሲዉ፣
ኮከብዋ በረኛችን አመዷ እና
የጠብቀዉ ወንድም ጮርነ ሁሉ ሳምንቱም ሙሉ ስዘጋጁበት ከርመዋል።ጮርነ ትንሽ ከኔ ጋር ፀበኛ ስለነበር እኔ በግጥሚያዉ እንዳልገባ ያደረገዉ ከፍተኝ ጥረት ተሳክቶለታል።ከላይ ሰፈር ልጆች
ቺንዲ፣
ላስላስ፣
ጠንበለል፣
ንፉቲ፣
ሲሬ፣
ግንቤ(ስሙን ቀስ ይጥራዉና ባለፈዉ በነሱ ሜዳ ስንጫወት ባደረገዉ ኮንጎ ጫማ ቅልጥመን ብሎኛል፤ዛሬማ ብሰለፍ ኖሮ ጉዱን አሳያለሁ ብዬ የታላቅ ወንድሜን ቦቲ ጫማ አድርገ ነበር የመጣሁት።)ሆነዉ በመለያቸዉ ላይ ስማቸዉን ፀፌዉ የጋሽ ሀይሌ ሜዳ ላይ ተሰብስበዋል።በነገራችሁ ላይ
የጋሽ ሀይሌ ሜዳ በኛ ሰፈር የኳስ ተንታኞች
አሊያን ዛሪና የምል ቅፅል ተሰጥቶት ነበር እኛ ግን ብዙም ስላልተመቸን ሜዳዉን የጋሽ ሀይሌ ሜዳ ብለን እንጠራዋለን።በዝህ ታላቅ የሰፈራችን ደርቢ ብዙ ተመልካች ይገኝል ተብሎ ይጠበቃል።ብያንስ ከ 20-34 ሰዉ ጫዋታዉን ለማዬት ትኬት እንደቆረጠ የጫዋታዉ ትኬት ቆራጭ
ሲስኮ ነግራናለች። የ'ኛ ደጋፊዎች ስለ'ኛ እየዘመሩ ነዉ እንደምታዉቁት የነ ግንቤ ቡድን ልጆች ሁሉ እረኞችና የመደበኛ ትምህርታቸዉን እንኳ ባግባቡ ያልተማሩና ያቋረጡ ናቸዉ፤የኛዎቹ ሁሉም ግን የ ፫ኛ ፬ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸዉ።